Skip to main content

የበጀት፣ ፋይናንስና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ

1.1 የክልሉ የበጀት፣ ፋናንስና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተሏቸዉ ቢሮዎች

.ፋይናንስ ቢሮ

.የገቢዎች ባለሥልጣን

. የፕላንና ልማት ቢሮ

. ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ሲሆን እንዲሁም ይህ ኮሚቴ ለሚከታተለዉ ቢሮ ተጠሪ የሆኑ ተቋማትንም ያጠቃልላል፡፡

1.2 የክልሉ የበጀት፣ ፋናንስና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተሉትን ተግባራት ያከናውናል፡፡

  •  በምክር ቤቱ ለክልሉ መንግሥት የተመደበ ማንኛውም በጀት በአግ ባቡ ስራ ላይ መዋሉን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፡፡
  • ኮሚቴው የዋና ኦዲተር ሪፖርትን ይመረምራል፡፡ በሚመረምርበት ወቅትም፤
  • የተመደበው በጀት ለታለመለት ዓላማና አገልግሎት ወጪ የተደረገ መሆኑን፣
  • ወጪው ስልጣን ባለው አካል የተረጋገጠ መሆኑን፣
  • የበጀት ዝውውር ሲኖር በፋይናንስ ሕጉ መሠረት መከናወኑን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፡፡
  • በምክር ቤቱ ትዕዛዝ በዋና ኦዲት /ቤት የተከናወነ የንብረት ኦዲት ውጤትን ይገመግማል
  • በማንኛውም መንግሥታዊ አካል በበጀት አመቱ ከተመደበው በላይ የበጀት አጠቃቀም ሲኖር ኮሚቴው ከበጀት በላይ ለማውጣት አስገዳጅ የሆነውን ምክንያት የማጣራትና አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘውም ሪፖርትና የውሣኔ ሃሳብ ለምክር ቤቱ የማቅረብ ኃላፊነት አለበት፡፡
  • ከኮሚቴው ተግባር ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የክልሉን ፖሊሲዎች፣ ሕጎች፣ ስትራቴጂዎች፣ ኘሮግራሞችና ዕቅዶች በአግባቡ ሥራ ላይ መዋላቸውን ይቆጣጠራል፡፡ ይከታተላል፡፡
  • የክልሉ መንግሥት ዓመታዊና ተጨማሪ በጀት በአግባቡ መጽደቁን እና ሥራ ላይ መዋሉን ያረጋግጣል፡፡
  • የክልሉ መንግሥት ገንዘብና ንብረት በአግባቡ መሰብሰቡን እና መጠበቁን መከታተል፡፡
  • ለክልሉ ከፌዴራል የሚሰጡ ድጎማዎችና ክልሉ ለዞንና ልዩ ወረዳ የሚሰጠው የበጀት ድጎማ በቀመሩ መሠረት መሆኑን ይከታተላል፡፡
  • በክልሉ ለታችኛዉ የአስተዳደር ዕርከን ዓመታዊ የሀብት ማከፋፈያ ቀመር ያዘጋጃል፤ለክልሉ ምክር ቤት እንዲጸድቅ ያቀርባል፡፡
  • የክልሉን ካፒታል ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ክትትልና ግምገማ ያደርጋል፤ወቅታዊ ሪፖርት በማዘጋጀት አግባብነት ላላቸዉ አካላት ያቀርባል፡፡
  • የክልሉን ዓመታዊ የሀብት ግመታ ሰነድ ያዘጋጃል፤ለክልሉ መስተዳደር ምክር ቤት በማቅርብ ያስፀድቃል፡፡